ራዕይ፣ ተልዕኮና ዕሴቶች
ራዕይ
በ2023 የሕገመንግስት የበላይነትና ፍትሐዊነትን በማረጋገጥ ሕብረብሔራዊ አንድነትና ዘላቂ ሰላም የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን መገንባት፡
ተልዕኮ
ሕገ መንግሥቱን በመተርጎም፣ በመፈቃቀድና በእኩልነት ላይ የተመሠረተ የሕዝቦች አንድነት ሥር እንዲሰድና እንዲዳብር በማድረግ፣ በክልሎች መካከል ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ግንኙነቶችን በማዳበር፣ ፍትሀዊና ውጤታማ የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ማከፋፈያ ቀመር በማዘጋጀትና በመወሰን፣ ሕግ ሊወጣላቸው የሚገቡ የፍትሐ ብሔር ጉዳዮችን በማጥናትና በመለየት፣ እንዲሁም ዜጎች ሕገ መንግሥቱን ጠንቅቀው አውቀው ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት በቁርጠኝነት መሥራት፣
ዕሴቶች
- ትክክለኛና አድልዎ የሌለበት ውሳኔ መስጠት፣
- በዘር፣ በሃይማኖት፣ በፆታና በፖለቲካ አመለካከት ወዘተ... ልዩነት ሳይደረግ ሁሉንም በእኩልነት ማገልገል፣
- የሚመለከታቸውን ሁሉ በማሳተፍ የተለያዩ ሃሳቦችና አመለካከቶች በነጻ እንዲንሸራሸሩ ማድረግ፣
- የምክር ቤቱን ባለድርሻዎች በቅንነት ማገልገል፣
- ባለድርሻዎችን ሊያሳትፍ በሚያስችል ግልጽ አሰራር ላይ ተመስርቶ ማከናወንና የሚያስተላልፋቸውን ውሳኔዎች በግልፅ ማድረግ፣
- ለሕገ መንግሥቱ፣ ለሕዝቡ፣ ለሕሊናቸው፣ እንዲሁም ም/ቤቱ ለሚያስተላልፋቸው ውሳኔዎች ታማኝና ተገዢ መሆን፣
- ማናቸውንም አመለካከቶችና ልዩነቶች በመቻቻልና በመከባበር መንፈስ ማስተናገድ፣
- አቤቱታዎችን በሕገ መንግሥቱና በአዋጅ በተቀመጡ
የጽህፈት ቤቱ - ዓላማ, ስልጣንና, ተግባር
ከ1993 ዓ.ም በፊት ምክር ቤት የራሱ ጽሕፈት ቤት አልነበረውም፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት የተቋቋመው በ1993 ዓ.ም. ነበር፡፡ ነገር ግን እስከ 2000 ዓ.ም ድረስ የሕግ ሰውነት አልነበረውም፡፡ ሕግ ሰውነት ያገኘው በአዋጅ ቁጥር 556/2000 ነው፡፡ ጽሕፈት ቤቱ ተጠሪነቱ ለአፈ ጉባኤው ሲሆን የሚከተሉት ተግባርና ኃላፊነቶች አሉት፡
1 ለምክር ቤቱና ምክር ቤቱ ለሚያቋቁማቸው ኮሚቴዎች፣ ለአፈ-ጉባዔዎች፣ ለምክር ቤቱ አባላት አጠቃላይ...