Vision, Mission, Values
ራዕይ
በሕገ መንግሥቱ ለተረጋገጠው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች እኩልነት፣ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ዲሞክራሲያዊ አንድነት ዘብ የቆመ ምክር ቤት ሆኖ ማየት፣
ተልዕኮ
ሕገ-መንግስቱን በመተርጎም፣ የራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎችን ውሳኔ በመስጠት፣ ፍትሃዊ የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ማከፋፈያ ቀመር በመወሰን፣ ሊፈጠሩ ለሚችሉ ግጭቶችንና አለመግባባቶች ውሳኔ በመስጠት፣ በየሰመረ የመንግሥታት ግንኙነት በማዳበር፣ በሕ/ተ/ም/ቤት ሕግ ሊወጣላቸው የሚገቡ የፍትሃ ብሔር ጉዳዮችን በመለየት፣ ንቃተ ሕገ-መንግሥት እንዲፈጠር በማድረግ፣ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ግንኙነትን በማጠናከር ዴሞክራሲያዊ አንድነት ሥር እንዲሰድ ማድረግ፣
ዕሴቶች
ሀ/ ሕገ መንግሥታዊነት፣
ለ/ ዴሞክራሲያዊነት፣
ሐ/ ፍትሃዊነት እና/ወይም እኩልነት፣
መ/ ተዓማኒነት፣
ሠ/ አሳታፊነት፣
ረ/ አጋርነት፣
ሰ/ ግልጸኝነት፣
ሸ/ ወቅታዊ ምላሽ፣
Adress
Telephone: +251-111-242-301/3
Telephone: +251-111-242-309
Telephone: +251-111-223-322
Fax: +251-111-242-304/8
Fax: +251-111-241-208
P.O.Box: 20212/1000
Addis Ababa, Ethiopia
Establishment & Major Powers & Duties of the House
የፌዴሬሽን ምክር ቤት በኢፌዴ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 61 የተመሠረተ፣ በአገራችን ክልሎች የሚገኙ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ውክልና የሚረጋገጥበት የፌዴራል ምክር ቤት ነው፡፡ በዚህ ምክር ቤት እያንዳንዱ ብሔር፣ ብሔረሰብና ሕዝብ ቢያንስ በአንድ ተወካይ የሚወከል ሲሆን ለያንዳንዱ አንድ ሚሊየን ሕዝብ ተጨማሪ አንድ ወኪል ይኖረዋል፡፡ የፌዴሬሽኑ ምክር ቤት አባላት የሚመረጡት በክልል ምክር ቤቶች አማካይነት ነው፡፡ ምርጫው በቀጥታ አሊያም ደግሞ በተዘዋዋሪ ሊካሄድ ይችላል፤ ይህም ማለት የክልል ምክር ቤቶች አባላቱን በራሳቸው ወይም በቀጥታ በሚደረግ ሕዝባዊ ምርጫ እንዲመረጡ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ በ5ኛው የምክር ቤት ዘመን፣ ምክር ቤቱ በአጠቃላይ 153 አባላት የነበሩት ሲሆን 76 ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችም ተወክለዋል፡፡
የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 62 እና በአዋጅ ቁጥር 251/93 መሠረት በርካታ...
History of House of Federation
የፌዴሬሽን ምክር ቤት የተመሠረተው የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት በጸደቀበት 1987 ዓ.ም. ነው፡፡ ምክር ቤቱ ከተመሠረተ ጀምሮ አምስተኛ የምክር ቤት ዘመን በማገባደድ ላይ ነው፡፡ በምክር ቤቱ ባለፉት አምስት የምክር ቤት ዘመን የሥራ ዓመታት የነበረው የአባላት ውክልና በየጊዜው እያደገ እና እየሰፋ መጥቷል፡፡ በመጀመሪያው የምክር ቤት ዘመን (ከ1987 ዓ.ም እስከ 1992 ዓ.ም.) 108 አባላት የነበሩት ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 7ቱ ሴቶች ነበሩ፡፡ በሁለተኛው የምክር ቤት ዘመን (ከ1993 ዓ.ም እስከ 1997 ዓ.ም.)የአባላቱ ቁጥር ወደ 112 ያደገ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የሴቶች ብዛት 8 ሆኖ ነበር፡፡ በሦስተኛው የምክር ቤት ዘመን (ከ1998 ዓ.ም እስከ 2002 ዓ.ም.)የምክር ቤቱ አባላት ብዛት 121 ሲደርስየሴቶች ቁጥርም 22 ደርሷል፡፡ በአራተኛው የምክር ቤት ዘመን (ከ2003 ዓ.ም.እስከ 2007 ዓ.ም.) የምክር ቤቱ አባላት 135 ሲሆን...